A new petition has started>> a letter to prime minister meles zenawi

A new petition has started. Please read the following pettion letter. Then click the link and sign the on line petition. (The letter is written in diplomatic way to assist the work of our committee).
ለክቡር አቶ መለስ ዜናዊ
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ ጠቅላይ ሚኒስትር
አዲስ አበባ
አቤት ባዮች እኛ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች ስንሆን የአቤቱታችንን ፍሬ ነገር እንደሚከተለው አቅርበናል።
በኢትዮጵያ ህዝቦች ይሁንታና ንቁ ተሳትፎ የጸደቀው የኢ.ፌዴ.ሪ ህገ-መንግስት ዜጎች እምነታቸውን በነጻነት ማንጸባረቅና የአምልኮ ስርዓታቸውን ያለ አንዳች ገደብ ማከናወን እንደሚችሉ የታወጀበት የህዝቦቻችን የቃል-ኪዳን ሰነድ መሆኑ ይታወቃል። የኢትዮጵያ ሙስሊሞችም በህገ-መንግስቱ በተደነገገው መሰረት የአምልኮ ስርዓታቸውን በነጻነት ሲያከናውኑ ቆይተዋል። ሙስሊሞች በሙሉ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚወከሉበትን የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በማቋቋም ለእምነታቸውም ሆነ ለሀገራቸው የሚጠቅሙ ተግባራትንም ሲፈጽሙ ኑረዋል። ከጥቂት ዓመታት ወዲህ ግን በሀገሪቱ ሙስሊሞች የእምነት ነጻነትና የዜግነት መብቶች ላይ ታላቅ አደጋ የደቀነ እንቅስቃሴ እየተካሄደ ይገኛል። ይህንን እንቅስቃሴ ፊታውራሪ ሆነው በመምራት ላይ ያሉትም ህዝበ ሙስሊሙ ባልተሳተፈበት ሁኔታ ተመራርጠው የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትን በሞኖፖል የተቆጣጠሩት ጥቂት የአመራር አካላት ናቸው።
እነኝህ ግለሰቦች ከሀይማኖታዊ አባት በማይጠበቅ መልኩ በቡድንተኝነት ስሜት እርስ በራሳቸው ሲጠቃቀሙና ሌሎችን እያሳደዱ ሲያጠቁት ከርመዋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ለሀገራችን ሙስሊሞች ባዳ የሆነውና “አል-አሕባሽ” የሚባለው የእምነት አንጃ የሚያራምደውን ርዕዮት እንድንከተል ለማድረግ መጠነ ሰፊ እንቅስቃሴ እያደረጉ ይገኛሉ። ህዝበ ሙስሊሙ በማያውቀው መድረክ በወሰኑት ውሳኔ የሀገራችንን መስጊዶችና መድረሳዎች በጠቅላላ በዚህ አንጃ ተከታዮች ቁጥጥር ስር ለማስገባት ሰፊ ዘመቻ እየተካሄደ ነው።። የነርሱን ህገ-ወጥ አካሄድ የማይቀበሉትን በሙሉ በጽንፈኝት በመፈረጅ የጥቃት በትራቸውን ያሳርፉበታል። ለዚህ እንዲያመቻቸው በማሰብም “ወሀቢያ” እና “ኸዋሪጃ” ለተሰኙ አደናጋሪ ቃላት ያሻቸውን ትርጉም እየሰጡ በጨዋነትና በመቻቻል ባህላቸው ዓይነተኛ ተጠቃሽ የሆኑትን የሀገራችንን ሙስሊሞች በአደባባይ በአክራሪነት ፈርጀዋል። በቅርበት ለሚያውቋቸው የመንግስት ባለስልጣናት የሀሰት መረጃዎችን በመስጠት በኮሌጆችና በዩኒቨርሲቲዎች በሚማሩ ሙስሊም ወጣቶች ላይ ልዩ ልዩ እቀባዎች እንዲጣሉ አድርገዋል። በዚህም ወጣቶቻችን አምልኮአቸውን በነጻነት እንዳያካሂዱ ከፍተኛ ችግር ተፈጥሯል።
ክቡር ሆይ!
የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አመራር አካላት የሚያካሄዱትንና አድማሱን ከጊዜ ወደ ጊዜ በማስፋት ላይ ያለውን ይህንን ህገ-ወጥ ዘመቻ በጭምምታም ቢሆን ያውቃታል ብለን እንገምታለን። ሆኖም ከታች ካሉት የመንግስት መዋቅሮች ጋር በመወያየት ችግራችንን ልንፈታው እንችላለን በሚል ተስፋና እምነት ጉዳዩን ወደርስዎ ከማምጣት ተቆጥበን ቆይተናል። በተጨማሪም በረጅሙ የኢትዮጵያ ታሪክ የህዝበ ሙስሊሙን ሙሉ የእምነት መብት በይፋ በመቀበል ብቸኛ በሆነው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ መንግስትና በሙስሊም ዜጎቹ መካከል ጸንቶ ያለውን ወዳጅነት ለመሸርሸር የሚፈልጉ ሀይሎች ነገሩን እያራገቡ የሀሰት ፕሮፓጋንዳ ሊነዙበት ይችላሉ በሚል ፍራቻ ወደርስዎ አላቀረብነውም። ይሁንና ከታች ያሉት የመንግስት አካላት እንደተመኘነው ችግራችንን ሊፈቱልን አልቻሉም። ከጥቂት ሳምንታት ወዲህ ደግሞ የእስልምና ጉዳዮች ም/ቤት አመራሮች የአወሊያ እስላማዊ ኮሌጅን የመሳሰሉ የእምነት ተቋሞቻችንን እራሳቸው ባመጡት አዲስ አንጃ ስር ለማስገባት የሚያደርጉት ህገ-ወጥ እንቅስቃሴ ህሊናችንን እረፍት ነስቶታል። ስለሆነም ለችግራችን አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጠን ለመጠየቅ አቤቱታችንን ለርስዎ ማቅረቡ አማራጭ የሌለው መንገድ ሆኖ አግኝተነዋል። በዚሁ መሰረት ክቡርነትዎ ካለዎት ህገ-መንግስታዊ ሃላፊነት በመነሳት ጉዳዩን አይተው
1. የም/ቤቱ አመራሮች ለ“አል-አሕባሽ” አንጃ በመወገን ሙስሊሙ በጠቅላላ የአንጃው ተከታይ እንዲሆን ለማድረግ በሚል የሚያካሄዱትን ህገ-ወጥ እንቅስቃሴ እንዲያቆሙልን
2. የም/ቤቱ አመራሮችና ተከታዮቻቸው በወሰዷቸው ህገ-ወጥ እርምጃዎች ከስራ ገበታቸው የተፈናቀሉ ዜጎች በአፋጣኝ ወደ ስራ ገበታቸው እንዲመለሱ፣
3. በም/ቤቱ አመራሮች የተዘጉት የአወሊያ እስላማዊ ኮሌጅና ሌሎች እስላማዊ ተቋማት ተከፍተው መደበኛ ስራቸውን እንዲጀምሩ
4. የም/ቤቱ አመራር አባላት ምርጫ የሁሉንም ሙስሊሞች ፍላጎት በሚያሟላ መልኩ በአስቸኳይ እንዲካሄድ
5. የም/ቤቱ አመራር አካላት በተለያዩ መድረኮች ሲሰጧቸው ለነበሩት የተሳሳቱ መግለጫዎች ሙስሊሙን በይፋ ይቅርታ እንዲጠይቁ
የሚያዝ ቀጥተኛ አመራር እንዲሰጡልን፣ ይህንን ማድረጉ አስቸጋሪ ከሆነ ግን በህገ-መንግስቱ በተሰጠን መብት መሰረት ከ“አል- አሕባሽ” ጋር አንድ አይነት ርዕዮትና የእምነት ፍልስፍና የማንከተለው ብዙሀኑ ሙስሊሞች የምንሰባሰብበት አዲስ ምክር ቤት ለመመስረት እንድንችል ፈቃድ እንዲሰጠን በአክብሮት እንጠይቃለን።
ከሰላምታ ጋር
http://www.change.org/petitions/prime-minister-of-the-federal-democratic-republic-of-ethiopia-hear-the-voices-of-ethiopian-muslims


  • Abdu Banned

    arif naw

  • kibrom

    መጨረሻ ላይ የተፃፋውን ግን ዐልደግፈውም፡፡

  • siraj beyan

    the Question which is posted by my brothers is also my Question i am waiting a hopefull ansewer

  • sebrina

    ያ.....ረብ አላህ ሙስሊሙን ለድል ያብቃው......!!!!!!

  • adbu k

    ato biruk dinkem gazetenga ewunet ante neberik yemiteikew weis ende ahmedin yesetuhin neber yemitanebew tewakayochachinin endeza wede metfo aktacha /metfo lemanager/ sitiwetewitachew yeneberew le sheh ahmedin letebalew munafiks yemititeikew tiake ateh new weys tizaz tesetoh new ayegenzeb hilinahin ashetechih

  • abdulhafiz

    i saw it ist time on my link to facebook if it is what happned in the reall situation not only a pettition to hear our voice every muslim individual has to be responsibl for his religion by doing in respective to the hadith and the quran thought beacuse that is the way how muslim brotherhood and religion monothesism become strength, so i next to the voice of the right way muslim thought support it

  • bahrya

    yedresa lebruka fm 98.1 azegaga manewu leato ahmedin giza afah teyaza yahulu wera siwerulh andam giza tyaka yalteykwu manewu sarhan zengtehwu newu weys dagos yal rebat asharwuha afhan askfatwu yaskeruh macham besalm aymesalgnam yemuya gadathan yasresah betam betam yemtasazan sewu neha ibakah yemuya gadta mewetat kakateh tansha inkan yehgera fkera samat yasamah wedafit tansha asba ibakhannnnnnnnn!!

Related Articles

Latest Articles

Most Popular