warning !!! warning !!! ማስጠንቀቂያ!!! ማስጠንቀቂያ!!!

ምጻችን ይሰማ ►►ማስጠንቀቂያ!!! ማስጠንቀቂያ!!! ሙስሊሞች ሆይንቁ!!►► ሰላማዊ የመብት ትግላችንን አሁንም የቀጠልን ብንሆንም ብዙ ስራ እንደሚጠበቅብን ግልፅ ሆኗል፡፡ መጅሊስና አጋሮቹ አሁንም አልተኙልንም፡፡ አሁን በሚገኙት የመጅሊስ አመራር አባላት ተስፋ የቆረጠው ፌዴራል ጉዳዮች ምርጫ አይቀሬ መሆኑን ተረድቶ ሁሉንም ሊያባርራቸው ወስኗል፡፡ ነገር ግን ምርጫውን አሁንም በቁጥጥር ስር ለማዋል ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረጉ ይገኛሉ!!! ምርጫውን የሚያስፈጽም ‹‹ገለልተኛ›› ሰው ስላስፈለጋቸው ጥረታቸውን ቀጥለዋል፡፡ ይህንንም ለማሳካት የአህባሽ ስልጠና እንደገና ሊሰጡ ሲሆን ኦሮሚያ፣ ደቡብ ክልል፣ አማራ ክልልና አሁን ደግሞ በወሰኑት መሠረት በአዲስ አበባ በአጠቃላይ 15 ሺህ ሰው ያህል ለማሰልጠን ዝግጅት እያደረጉ ነው፡፡ አዲስ አበባን ሳይጨምር በክልሎቹ ለሥልጠና የተመረጡት 16 ያህል ቦታዎች ናቸው፡፡ ስልጠናው ላይ አህባሽ ላይ ለቀረቡት ውንጀላዎች ‹‹ምላሽ›› የሚሰጡ ሲሆን ስልጠናውን የሚወስዱት የመስጊድ ኢማሞችና ዱአቶች ናቸው፡፡ የአህባሽ ደጋፊ እንዲሆኑና ምርጫውን እንዲቆጣጠሩለት፣ ‹‹ወሃቢያ›› እንዳይመረጥ እንዲከላከሉለት ፌዴራል ጉዳዮች ቋምጧል!!! (መብቴን ያለ ሁሉ ለነሱ ወሃቢያ ነው!!!) በጀቱ በሙሉ በፌደራል ጉዳዮች ነው የሚሸፈነው፡፡ ታይም ቴብሉንም ሁሉ አውጥቶ ለመጅሊስ የላከው ፌዴራል ጉዳዮች ነው!!! ስልጠናውንም ሊጀምሩ ያሰቡበትን ጊዜ በማራዘም ሚያዝያ 10 እና 11 ሊጀምሩት ወስነዋል፡፡ በምርጫው በ‹‹ሱፊ›› እና ‹‹ወሃቢያ›› መካከል ቡድን ለመፍጠርና ክፍፍል ለመፍጠር ፈልገዋል!!! አላህ ስንት ተንኮላቸውን አፈረሰባቸው??? መቼ ይሆን ልብ የሚገዙት??? በክልሎች መጅሊስ ጠቅላይ ጉባኤ እየተካሄደ ሲሆን ትናንት በባህርዳር መስጊድ አስመርቀው ከፍተው ዛሬ ሲወያዩ ውለዋል፡፡ ስትራቴጂያቸውን ሲነድፉም ቆይተዋል፡፡ ኢህአዴግ አባላቱን ባለፉት ሁለት ቀናት በተለያየ ቦታ ሰብስቦ ሲያወያይ የቆየ ሲሆን በበርካታ ቦታዎች ከአባላቱ ተደጋጋሚ ተቃውሞ ሲቀርብበት ነበር፡፡ ነገር ግን በማስፈራራት እና እንቅስቃሴው የወሃቢይ አክራሪያን እንደሆነ በመናገር አንዳንድ አባላቱን ለማሸማቀቅ ‹‹ከሁለት አንዱን ምረጡ!›› እያለ ሲያስፈራራ ነበር፡፡ ጥናት ተብዬ ወረቀትም አቅርበዋል!!! በተለያዩ ቦታዎች የመጠይቅ ወረቀት (ኩዌሽነር) የበተኑ ሲሆን መንግስት ጣልቃ ገብቷል ወይ በሚል ለቀረበው ጥያቄ 99 በመቶው ‹‹አዎ! ጣልቃ ገብቷል!›› የሚል መልስ እንደሰጣቸውም ታውቋል!!! ግን እነሱ እውነት መስማት አይፈልጉም!! በተጨማሪም ከየቀበሌው 15 ሰዎችን ለምርጫው መልምለው ጨርሰዋል፡፡ የነሱ ፍላጎት ምርጫውን በቀበሌ አድርገው የሚፈልጉትን ሰው በገፍ ሊያሰርጉ ነው!!! እኛ ደግሞ መንፈሳዊ ማእከላችን መስጊድ እንጂ ቀበሌ ስላልሆነ ይህንን በፍጹም መቀበል የለብንም!!! መልካም የአላህ ባሪያዎች እና ታማኝ ሰዎቻችን የሚገኙት በመስጊድ ነውና ምርጫ በቀበሌ ምልመላ እንዳይሆንና ይህን መሰሉን ሸፍጥ እና መንግስታዊ ጣልቃ ገብነት ካሁኑ ለመከላከል ቁርጠኝነት ያሻናል!!! ፌዴራል ጉዳዮች ይህንኑ የሸፍጥ ስራውን በመቀጠል ለአውሮፓ ህብረት እና ለአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት ሪፖርት ያስገባ ሲሆን በሪፖርቱም አገራችን ውስጥ በእምነት ግጭት ምክንያት የተቃጠሉ ቤተ ክርስቲያናትን እና ሌሎች የተከሰቱ ግጭቶችን በመዘርዘር ‹‹ሁሉንም ያደረጉት እነዚሁ ወሃቢዮች ናቸው፡፡ አሁን ዋና መናኸሪያቸው አወሊያ ሲመታባቸው ነው መብታችን ተጣሰ እያሉ የሚረብሹት፡፡ አሁን ግን እርምጃ ልንወስድባቸው ስለሆነ ሰብአዊ መብት ጣስክ ብላችሁ እንዳትረብሹኝ›› ሲሉ አቅርበዋል!!! ተመልከቱ ምን ያህል ለእስልምና ያላቸው ጥላቻ አይን ያወጣ ውሸት ውስጥ እንደጨመራቸው!!! ሰላማዊ ዜጎቻቸውን ለማጥቃት እና ህገመንግስታዊ መብታቸውን በሰላማዊ መንገድ የጠየቁ ሰዎችን በአክራሪነትና በውሸት በመወንጀል የፈለጉትን ለማድረግ አረንጓዴ መብራት እንዲበራላቸው ውጭ ሃገር ይለማመጣሉ!!! ተመልከቱ ፌደራል ጉዳዮች እየሰራ ያለውን! አንድ ሺ አንድ ሴራቸውን እስካሁን የመለሰባቸው አላህ አሁንም ይመልስባቸዋል እንጂ እንደነሱ ቢሆንማ ሰማይ በታረሰ ነበር!!! አላሁ አክበር! አላህን የያዘ አይወድቅም!!! ወደአላህ እያለቀስን የቻልነውን ልፋት እና ስራ ሁሉ ማከናወን፣ ለዲናችን ዘብ መቆም አለብን!!! አላሁ አክበር!!! ከዚሁ ምርጫ ጋር በተያያዘ ፌደራል ጉዳዮች አራት ሰዎችን በፌደራል ደረጃ ታዛቢና ተቆጣጣሪ እንዲሆኑለት መርጧል፡፡ እነዚህም አራት ሰዎች የሀጂ ሳኒ ልጅ የሆኑት ሃጂ መሃመድ ኑር፣ ግራዝማች ሀዲስ ኑርሁሴን፣ ኢንጅነር ተማምና ሀጂ ፈድሉ ይባላሉ፡፡ (ግራዝማች ሃዲስ በ1987 ግርግር ዋነኛ ተዋናይ የነበሩና መጅሊስ የአወሊያውን ተቃውሞ እንዲያደበዝዙ የፈበረከው የሽማግሌ ቡድን አባል ናቸው!) ልብ እናድርግ ሙስሊሞች ሆይ! አስመራጭ ኮሚቴውን የሚመርጠው ፌደራል ጉዳዮችም ሆነ አሁን ያለው መጅሊስ አይደለም!!! የመምረጥ መብቱ የህዝበ ሙስሊሙ ነው! በመሆኑም እኛ ከምንመርጠው ውጪ የፈለገ ጥሩ የሚመስል ወይም የሆነ ሰው ቢመጣ በፍጹም አንቀበልም!!! ይህንን በፍጹም እንዳንረሳ!!!! ሰዎቹ ጥሩ ቢሆኑም እንኳ የምንመርጠው እኛ እንጂ መነግስት አይደለም፡፡ ስለዚህ ካሁኑ ለሌሎች በማሳወቅ ምርጫችንን ከጣልቃ ገብነት መከላከል አለብን!!! አላሁ አክበር!!! ከሐጅ ጋር በተያያዘ ሌላ ጉድ አለላችሁ! ፌደራል መጅሊሶች በሐጅ ጉዳይ ለመደራደርና ለመፈራረም ወደሳኡዲ ሊሄዱ ነው! ለጉዞው የሚሄዱት አራት ሰዎች ሲሆኑ አህመዲን አብዱላሂ፣ አዛም እና የሐጅ አስፈጻሚው አቶ አማን ሁሴን ይገኙበታል፡፡ እዚያ መሀመድኑር የሚባል ኢትዮጵያዊ ነው እስከዛሬ ሙስናውን፣ የቤት ኪራዩን ሁሉ ሲያመቻችላቸው የቆየው፡፡ ይህ ሰውዬ ለራሱም 6 አባዱላ ሚኒባስ ያለው ሀብታም ነው፡፡ የሃጅ ሙስና ዋና አመቻች እሱ ነው፡፡ ሳኡዲ ውስጥ ተቃውሞ ይገጥመናል ብለው ስለፈሩ ሙፍቲ ሃጂ ኡመርን ይዘው ሊሄዱ ነው ያሰቡት፡፡ እሳቸው ይስማሙ አይስማሙ ቁርጡን ያወቅኩት ነገር ባይኖርም ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሚገኘው የአራቱም ሰዎች ፓስፖርት ግን ባለፈው ጁሙኣ ቪዛ ተመቶበታል፡፡ (የሁሉም መጅሊስ አመራር አባላት ፓስፖርት ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ነው የሚቀመጠው!) ጉዞውም አፕል ሶስት ነው፡፡ ያሳዝናል! ሊባረሩ ጥቂት ጊዜ ቀርቷቸውም እንኳን ከሌብነታቸው መቆጠብ አይፈልጉም!!! አላሁ አክበር! ምን አይነት የብር ፍቅር ነው የያዛቸው???!!! ሙስሊም ወንድሞቼ እና እህቶቼ ሆይ! እስቲ እናስተውል… እኛ አወሊያ ተሰብስበን መፈክር ስላሰማን ብቻ ብዙ የሰራን መስሎን እንረካለን፡፡ አልሀምዱሊላህ አላህ አጅራችንን ያበዛዋል፡፡ ሙስሊሞችን ጠምዶ የያዘው ዶክተር ሽፈራውና ድርጅቱ ግን በርካታ ስራ በሚሊዮን ብር በጀት እየሰራ ነው!!! እኛ በጥቂት ነገር ስንረካ እነሱ ግን ወስጥ ለውስጥ ብዙ ድንጋይ ይፈነቅላሉ፡፡ አላህ እንደ የእጁጅና መእጁጅ ቁፋሮ መና እያደረገባቸው እንጂ!!! አሁንም ቢሆን ብዙ ስራ ይጠበቅብናል፡፡ ገና አስቸጋሪውን ትግል እየጀመርነው ነው! ተስፋ በፍጹም አንቆርጥም!!! እስከመጨረሻው አላህ ያደርሰናል… እስካሁንስ እዚህ የደረስነው በአላህ ፕሮግራም እንጂ መች በእኛ ልፋት ሆነና!!! ከምንጊዜውም በበለጠ ምርጫውን ለመጠምዘዝ የሚካሄዱትን ሸፍጦች ለመቃወም እና ሁሌም በሰላማዊና በሰላማዊ መንገድ ብቻ መብታችንን ለመጠቀም ቁርጠኛ መሆን አለብን!!! እኔ ይኸው ለእናንተ መረጃውን በማድረስ ሃላፊነቴን ተወጥቻለሁ! ሁላችሁም ይህን ፅሁፍ ታግ እና ሼር በማድረግ፣ ፕሪንት አድርጎ በፎቶኮፒ ለሰዎች በማዳረስ በትእግስት ሃላፊነታችሁን ተወጡ!!! ‹‹አላህ ከትእግስተኞች ጋር ነውና!›› ‹‹የአላህን ሃይማኖት ብትረዱ አላህም ይረዳችኋል፡፡›› ቅዱስ ቁርአን
  • Sebrina Ahmed Banned

    Allah yeterachiwn emnet(Islamin) be hakegna meriwoch yastedadrat!! Amen!!

Related Articles

Latest Articles

Most Popular